የቢሮ ኃላፊ መልዕክት

ሀገረፅዮን አበበ
የስራ ፣ ክህሎትና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ኃላፊ
የሲዳማ ብ/ክ/መ/ስ/ክ/ኢ/ል/ቢሮ እንደ ቢሮ የተቋቋመው በ2014 ዓ.ም ሲሆን ሶስት ዋና ዋና ዘርፎችን ማለትም የሙያ ስልጠና እና ኢንተርፕራይዞች ልማት ዘርፍን፣ የስራ እድል ፈጠራ ዘርፍን እና አሰሪና ሰራተኛ ልማት ዘርፍን አካቶ በመያዝ ለክልሉ ብሎም ለሀገር አገልግሎት ሲሰጥ ቆይቶአል፡፡
አሰሪና ሰራተኛ ልማት ዘርፍ ከስራ፣ ከሰራተኛ ገበያ መረጃ፣ ከኢንዱስትሪ ግንኙነት እንዲሁም ከስራ ደህንነትና ከጤና ጋር በተያያዙ ጉዳዮች ላይ ሃላፊነትን ወስዶ ይሰራል።በአሰሪና በሰራተኞች መካከል ያለውን የሁለትዮሽ ግንኙነት እንዲሁም በአሰሪ፣ በሠራተኛና በመንግሥት መካከል ያለውን የሦስትዮሽ ግንኙነትን የማጠናከር ተግባራትን ያከናውናል፡፡ የግሉ ሴክተር የአሰሪና የሠራተኛ ግንኙነት ለመምራት የወጡ ፖሊሲዎች እና የሕግ ማዕቀፎች በክልሉ ተግባራዊ መሆናቸውን በበላይነት ይከታተላል፡፡
ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ለአንድ ሀገር ክህሎት፣መልካም አመለካከት እና እውቀት ያላቸውን ወጣቶች የማፍራት ዓላማ ያለው የትምህርት ስርዓት አካል ነው። ኢትዮጵያን ጨምሮ በማደግ ላይ ያሉ ሀገራት TVETን ለኢኮኖሚ ዕድገትና ሥራ አጥነትን ለመቀነስ ዋና መሳሪያ አድርገው ይጠቀሙበታል፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ...ዜናዎች

የሪፖርቱ ግምገማ መድረክ የመሩት የሲዳማ ክልል ምክርቤት የከተማና መሠረት ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ስብሳቢ ክብረት ወ/ሮ ምንትዋብ ገ/መሰቀል ቢሮው የአመቱ እቅድና ትግበራ በጥልቀት የገመገሙ ስሆን በግምገማው በአመቱ የታዩ ውጤቶች ተሰፋ የሚሰጥና በሁሉም ዘረፍ ከእቅዱ በላይ ማሳካት መቻሉ መየት ችለናል በለዋል ።

ደቡባዊ ሲዳማ ዞን ለ ኢንተርፕራይዞች የገበያ ትስስር ለመፍጠር ባዛርና ኤግዚቢሽን መክፈቱን የክልሉ ሥራና ክህሎት ቢሮ ገለፀ ።

የምክር ቤቱ አፌ ጉባኤ ክብሪት ወ/ሮ ፋንታዬ ከበደና ምክትል አፌ ጉባኤ ክቡር አቶ ዘነበ ዘርፉን ጨምሮ የምክር ቤቱ ቋሚ ኮሚቴ አመራሮች በማዕከላዊ ሲዳማ ዞን እና በደቡባዊ ሲዳማ ዞን ተገኝተው የሥራና ክህሎት ቢሮ በኩል የተሰሩ ስራዎችን ተዘዋውሮ እየተመለከቱ ይገኛሉ ።
ኃላፊዎች

ፍስሀ ፍቾላ ባኩሎ
የቢሮ ምክትል ኃላፊ እና የሙያ ስልጠና እና ኢንተርፕራይዞች ድጋፍ ዘርፍ ኃላፊ

ከፍያለው ከበደ
የቢሮ ምክትል ኃላፊ እና የሥራ እድል ፈጠራ ልማት ዘርፍ ኃላፊ

ዶ/ር ማቴ መንገሻ
የቢሮ ምክትል ኃላፊ እና አሠሪና ሠራተኛ ልማት ዘርፍ ኃላፊ

አዝመራ አመኖ
የቢሮ ምክትል ኃላፊ ማዕረግ የአስተዳደር እና ፋይናንስ ዘርፍ ኃላፊ

ስለሺ ሱራፌል ጤካሞ
የግዥ፣ፋይናንስ እና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር
