የቢሮ ኃላፊ መልዕክት


ሀገረፅዮን አበበ

የስራ ፣ ክህሎትና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ኃላፊ

የሲዳማ ብ/ክ/መ/ስ/ክ/ኢ/ል/ቢሮ እንደ ቢሮ የተቋቋመው በ2014 ዓ.ም ሲሆን ሶስት ዋና ዋና ዘርፎችን ማለትም የሙያ ስልጠና እና ኢንተርፕራይዞች ልማት ዘርፍን፣ የስራ እድል ፈጠራ ዘርፍን እና አሰሪና ሰራተኛ ልማት ዘርፍን አካቶ በመያዝ ለክልሉ ብሎም ለሀገር አገልግሎት ሲሰጥ ቆይቶአል፡፡

አሰሪና ሰራተኛ ልማት ዘርፍ ከስራ፣ ከሰራተኛ ገበያ መረጃ፣ ከኢንዱስትሪ ግንኙነት እንዲሁም ከስራ ደህንነትና ከጤና ጋር በተያያዙ ጉዳዮች ላይ ሃላፊነትን ወስዶ ይሰራል።በአሰሪና በሰራተኞች መካከል ያለውን የሁለትዮሽ ግንኙነት እንዲሁም በአሰሪ፣ በሠራተኛና በመንግሥት መካከል ያለውን የሦስትዮሽ ግንኙነትን የማጠናከር ተግባራትን ያከናውናል፡፡ የግሉ ሴክተር የአሰሪና የሠራተኛ ግንኙነት ለመምራት የወጡ ፖሊሲዎች እና የሕግ ማዕቀፎች በክልሉ ተግባራዊ መሆናቸውን በበላይነት ይከታተላል፡፡

ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ለአንድ ሀገር ክህሎት፣መልካም አመለካከት እና እውቀት ያላቸውን ወጣቶች የማፍራት ዓላማ ያለው የትምህርት ስርዓት አካል ነው። ኢትዮጵያን ጨምሮ በማደግ ላይ ያሉ ሀገራት TVETን ለኢኮኖሚ ዕድገትና ሥራ አጥነትን ለመቀነስ ዋና መሳሪያ አድርገው ይጠቀሙበታል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ...

ዜናዎች

የሲዳማ ክልል የሥራ ክህሎትና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ የሁለተኛ ዙር በዘመቻ ለአንድ ወር የሚቆይ ከዞን እስከ ወራዳና ቀበሌ ድረስ የድጋፍ ክትትል ስምሪት ዙሪያ ለአመራሮችና ለሠራተኞች የኦሬንቴሺን መድረክ አካሄደ ።

የሲዳማ ክልል ማዕከላዊ ሲዳማ ዞን ሻፋሞ ወረዳ ወጣቶች መንግስት ያመቻቸውን እድል ተጠቅመው በኢንተርፕራይዝ ተደራጅተው ሀብት ማፍራት የቻሉትን የስራ እንቅስቃሴ ጉብኝት ማድረጋቸውን ቢሮ ገለፀ

የሲዳማ ክልል የሥራ ክህሎትና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ በሁሉም ዘርፍ የተሻለ ውጤት ለማምጣትና የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ 2ኛ ዙር በዘመቻ ድጋፍና ክትትል ከዞን ፣ ወረዳና እስከ ቀበሌ ድረስ ለ30 ተከታታይ ቀናት የሚቆየውን ደቡባዊ ሲዳማ ዞን አመራርና ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር የጋራ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄደዋል ።

ኃላፊዎች

ፍስሀ ፍቾላ ባኩሎ

የቢሮ ምክትል ኃላፊ እና የሙያ ስልጠና እና ኢንተርፕራይዞች ድጋፍ ዘርፍ ኃላፊ

ከፍያለው ከበደ

የቢሮ ምክትል ኃላፊ እና የሥራ እድል ፈጠራ ልማት ዘርፍ ኃላፊ

ዶ/ር ማቴ መንገሻ

የቢሮ ምክትል ኃላፊ እና አሠሪና ሠራተኛ ልማት ዘርፍ ኃላፊ

አዝመራ አመኖ

የቢሮ ምክትል ኃላፊ ማዕረግ የአስተዳደር እና ፋይናንስ ዘርፍ ኃላፊ

ስለሺ ሱራፌል ጤካሞ

የግዥ፣ፋይናንስ እና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር

ብርሃኑ ያዕቆብ

የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር