የቢሮ ኃላፊ መልዕክት


ሀገረፅዮን አበበ

የስራ ፣ ክህሎትና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ኃላፊ

የሲዳማ ብ/ክ/መ/ስ/ክ/ኢ/ል/ቢሮ እንደ ቢሮ የተቋቋመው በ2014 ዓ.ም ሲሆን ሶስት ዋና ዋና ዘርፎችን ማለትም የሙያ ስልጠና እና ኢንተርፕራይዞች ልማት ዘርፍን፣ የስራ እድል ፈጠራ ዘርፍን እና አሰሪና ሰራተኛ ልማት ዘርፍን አካቶ በመያዝ ለክልሉ ብሎም ለሀገር አገልግሎት ሲሰጥ ቆይቶአል፡፡

አሰሪና ሰራተኛ ልማት ዘርፍ ከስራ፣ ከሰራተኛ ገበያ መረጃ፣ ከኢንዱስትሪ ግንኙነት እንዲሁም ከስራ ደህንነትና ከጤና ጋር በተያያዙ ጉዳዮች ላይ ሃላፊነትን ወስዶ ይሰራል።በአሰሪና በሰራተኞች መካከል ያለውን የሁለትዮሽ ግንኙነት እንዲሁም በአሰሪ፣ በሠራተኛና በመንግሥት መካከል ያለውን የሦስትዮሽ ግንኙነትን የማጠናከር ተግባራትን ያከናውናል፡፡ የግሉ ሴክተር የአሰሪና የሠራተኛ ግንኙነት ለመምራት የወጡ ፖሊሲዎች እና የሕግ ማዕቀፎች በክልሉ ተግባራዊ መሆናቸውን በበላይነት ይከታተላል፡፡

ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ለአንድ ሀገር ክህሎት፣መልካም አመለካከት እና እውቀት ያላቸውን ወጣቶች የማፍራት ዓላማ ያለው የትምህርት ስርዓት አካል ነው። ኢትዮጵያን ጨምሮ በማደግ ላይ ያሉ ሀገራት TVETን ለኢኮኖሚ ዕድገትና ሥራ አጥነትን ለመቀነስ ዋና መሳሪያ አድርገው ይጠቀሙበታል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ...

ዜናዎች

የሲዳማ ክልል ምክር ቤት የከተማና መሰረተ ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ 2017 የበጀት አመት የሥራ ክህሎትና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ የ6 ወር የእቅድ አፈጻጸም ገመገሙ::

የእቅድ አፈጻጸም መድረኩን የመሩት የከተማና መሰረተ ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ክብርት ወ/ሮ ምንትዋብ ገ/መስቀል የ2017 በጀት አመት የቢሮው የ6 ወር የአፈፃፀም በዝርዝር ገምግሟል ።

ወጣቶችን የኢኮኖሚ ተጠቃሚ ለማድረግ በልዩ ትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ ሲዳማ ክልል የሥራ ክህሎትና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ገለፀ ።

ቢሮው ሰሜናዊ ሲዳማ ዞን ማልጋ ወረዳ በመንግሥት ድጋፍ በተለያዩ ሥራ ዘርፍ የተሰማሩ ወጣቶች የሥራ እንቅስቃሴ ጉብኝት በማድረግ ከወረዳ አመራሮች ጋር የሥራ አፈጻጸም ገምግሟል ።

የሲዳማ ክልል የፖለቲካ አመራሮች በሥራ እድል ፈጠራ ስራ ላይ የሰጠው ትኩረት ለሌሎች ተሞክሮ የሚሆን መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚንስትር ድኤታ ክቡር ዶ/ር ተሻለ በሬቻ ገለፁ

ኃላፊዎች

ፍስሀ ፍቾላ ባኩሎ

የቢሮ ምክትል ኃላፊ እና የሙያ ስልጠና እና ኢንተርፕራይዞች ድጋፍ ዘርፍ ኃላፊ

ከፍያለው ከበደ

የቢሮ ምክትል ኃላፊ እና የሥራ እድል ፈጠራ ልማት ዘርፍ ኃላፊ

ዶ/ር ማቴ መንገሻ

የቢሮ ምክትል ኃላፊ እና አሠሪና ሠራተኛ ልማት ዘርፍ ኃላፊ

አዝመራ አመኖ

የቢሮ ምክትል ኃላፊ ማዕረግ የአስተዳደር እና ፋይናንስ ዘርፍ ኃላፊ

ስለሺ ሱራፌል ጤካሞ

የግዥ፣ፋይናንስ እና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር

ብርሃኑ ያዕቆብ

የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር