የቢሮ ኃላፊ መልዕክት


ሀገረፅዮን አበበ

የስራ ፣ ክህሎትና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ኃላፊ

የሲዳማ ብ/ክ/መ/ስ/ክ/ኢ/ል/ቢሮ እንደ ቢሮ የተቋቋመው በ2014 ዓ.ም ሲሆን ሶስት ዋና ዋና ዘርፎችን ማለትም የሙያ ስልጠና እና ኢንተርፕራይዞች ልማት ዘርፍን፣ የስራ እድል ፈጠራ ዘርፍን እና አሰሪና ሰራተኛ ልማት ዘርፍን አካቶ በመያዝ ለክልሉ ብሎም ለሀገር አገልግሎት ሲሰጥ ቆይቶአል፡፡

አሰሪና ሰራተኛ ልማት ዘርፍ ከስራ፣ ከሰራተኛ ገበያ መረጃ፣ ከኢንዱስትሪ ግንኙነት እንዲሁም ከስራ ደህንነትና ከጤና ጋር በተያያዙ ጉዳዮች ላይ ሃላፊነትን ወስዶ ይሰራል።በአሰሪና በሰራተኞች መካከል ያለውን የሁለትዮሽ ግንኙነት እንዲሁም በአሰሪ፣ በሠራተኛና በመንግሥት መካከል ያለውን የሦስትዮሽ ግንኙነትን የማጠናከር ተግባራትን ያከናውናል፡፡ የግሉ ሴክተር የአሰሪና የሠራተኛ ግንኙነት ለመምራት የወጡ ፖሊሲዎች እና የሕግ ማዕቀፎች በክልሉ ተግባራዊ መሆናቸውን በበላይነት ይከታተላል፡፡

ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ለአንድ ሀገር ክህሎት፣መልካም አመለካከት እና እውቀት ያላቸውን ወጣቶች የማፍራት ዓላማ ያለው የትምህርት ስርዓት አካል ነው። ኢትዮጵያን ጨምሮ በማደግ ላይ ያሉ ሀገራት TVETን ለኢኮኖሚ ዕድገትና ሥራ አጥነትን ለመቀነስ ዋና መሳሪያ አድርገው ይጠቀሙበታል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ...

ዜናዎች

Dijitaale Gashshooti 2030 Aana Qoqqowu Massagaanora Huwanyoote Kalaqate Bare Harinsi.

በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች የሚመራ የድጋፍና ክትትል ቡድን ወደ ሲዳማ ክልል ገቡ ።

ሀዋሳ: ህዳር 22/2017ዓ.ም የቢሮው ህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት

በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሚኒስትር ድኤታ ክቡር ዶ/ር ተሻለ በሬቻ የሚመራ የድጋፍና ክትትል ቡድን ከቢሮው የማኔጅመንት አባላት ጋር ውይይት አድርገዋል።

ፌዴራል የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የመጡ የድጋፍና ክትትል ቡድን የዳዬ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የስራ ጉብኝት በተጨማሪ ምስራቃዊ ሲዳማ ዞን በንሳ ወረዳ ዳዬ ከተማ እና ቦና ዙሪያ ወረዳ ተደራጅተው በተለያዩ ሥራ ላይ ተሰማርተው ያሉ ወጣቶች የሥራ እንቅስቃሴ ጉብኝት አድርጉ ።

ህዳር 23/2017ዓ.ም ቢሮው የህዝብ ግንኙነት ዳይረክቶሬት

ኃላፊዎች

ፍስሀ ፍቾላ ባኩሎ

የቢሮ ምክትል ኃላፊ እና የሙያ ስልጠና እና ኢንተርፕራይዞች ድጋፍ ዘርፍ ኃላፊ

ከፍያለው ከበደ

የቢሮ ምክትል ኃላፊ እና የሥራ እድል ፈጠራ ልማት ዘርፍ ኃላፊ

ዶ/ር ማቴ መንገሻ

የቢሮ ምክትል ኃላፊ እና አሠሪና ሠራተኛ ልማት ዘርፍ ኃላፊ

አዝመራ አመኖ

የቢሮ ምክትል ኃላፊ ማዕረግ የአስተዳደር እና ፋይናንስ ዘርፍ ኃላፊ

ስለሺ ሱራፌል ጤካሞ

የግዥ፣ፋይናንስ እና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር

ብርሃኑ ያዕቆብ

የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር