Skip to main content

ስራን ሳይንቁ መንግሥት ያመቻቸላቸው እድል መጠቀም የቻሉ ወጣቶች ከሰው እጅ ከማየት የራሳቸውን ሀብት ማፍራት ችለዋል።

image news

የሲዳማ ክልል ማዕከላዊ ሲዳማ ዞን ሻፋሞ ወረዳ ወጣቶች መንግስት ያመቻቸውን እድል ተጠቅመው በኢንተርፕራይዝ ተደራጅተው ሀብት ማፍራት የቻሉትን የስራ እንቅስቃሴ ጉብኝት ማድረጋቸውን ቢሮ ገለፀ

በጉብኝቱ ላይ የሲዳማ ክልል የሥራ ክህሎትና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ሀላፊ ክብርት ወ/ሮ ሀገረጽዮን አበበ ጨምሮ የቢሮ ምክትል ሀላፊዎችና የማኔጅመንት አባላት በመገኘት ወጣቶች ተደራጅተው በመስራት የራሳቸውን ሀብት ከማፍራት ባሻገር ለሌሎች የስራ እድል መፍጠር መቻላቸውን ማየት ተችሏል ።