Skip to main content

ወጣቶችን የኢኮኖሚ ተጠቃሚ ለማድረግ በልዩ ትኩረት እየተሠራ ነው፡፡

image news

ወጣቶችን የኢኮኖሚ ተጠቃሚ ለማድረግ በልዩ ትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝ ሲዳማ ክልል የሥራ ክህሎትና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ገለፀ ።

ቢሮው ሰሜናዊ ሲዳማ ዞን ማልጋ ወረዳ በመንግሥት ድጋፍ በተለያዩ ሥራ ዘርፍ የተሰማሩ ወጣቶች የሥራ እንቅስቃሴ ጉብኝት በማድረግ ከወረዳ አመራሮች ጋር የሥራ አፈጻጸም ገምግሟል ።

በጉብኝቱ ላይ የተገኙት ሲዳማ ክልል የሥራ ክህሎትና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ ሀላፊ ወይዘሮ ሀገረጽዮን አበበ የወጣቶችን የሥራ አጥነት ችግር ለመቅረፍና የኢኮኖሚ ተጠቃሚ ለማድረግ ቅድሚያ በመስጠት በተሠራው የወጣቶች ተጠቃሚነት እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል ።

ወጣቶች በተሰማሩበት የሥራ መስክ የተፈለገውን ውጤት ለማስመዝገብ ክህሎትን መሠረት ያደረገ የሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ ትኩረት በመስጠት ወጣቶች በተሰማሩበት ስራ መስክ ይበልጥ ውጤታማ መሆን መቻላቸውን ገልጸዋል ።