Skip to main content

በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች የሚመራ የድጋፍና ክትትል ቡድን ወደ ሲዳማ ክልል ገቡ ።

image news

በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች የሚመራ የድጋፍና ክትትል ቡድን ወደ ሲዳማ ክልል ገቡ ።

ሀዋሳ: ህዳር 22/2017ዓ.ም የቢሮው ህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት

በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሚኒስትር ድኤታ ክቡር ዶ/ር ተሻለ በሬቻ የሚመራ የድጋፍና ክትትል ቡድን ከቢሮው የማኔጅመንት አባላት ጋር ውይይት አድርገዋል።

ድጋፍና ክትትል የሚያደርገው ቡድን በሲዳማ ክልል በአራት (4) ወራት ውስጥ በክልሉ የተሰሩ ስራዎችን ምልከታ እንደሚያደርጉ ተገልጿል።

ቡድኑ በመስክ ምልከታው ከክህሎት ልማት፣ ሥራ ዕድል ፈጠራ፣ አሠሪና ሠራተኛ ግንኙት እና ከተቋማት ግንባታ አኳያ የተሰሩ ሥራዎችን እስከታችኛው የዘርፉ መዋቅር ድረስ በመውረድ የግል ኮሌጆችንና የመንግስት የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማትን፣ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ማዕከላትን፣ ኢንተርፕራይዞችን፣ የገጠር ሥራ ዕድል ፈጠራ ሥራንና ኢንዱስትሪዎችን ተዘዋውሮ እንደሚመለከት ክቡር ዶ/ር ተሻለ በሬቻ ገልጸዋል ።